ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች...
ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ማክስኞ ግንቦት 18 በርካታ ህዝብ የሚታደምበት የህዝብ ንቅናቄ በመስቀል አደባባይ ይደረጋል። በመሆኑም፣ ፕሮግሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የሚከተሉት መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፦ • ከመገናኛ በባንቢስ ሱፐር ማርኬት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ ላይ • ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ጥላሁን አደባባይ ወይም መሿለኪያ ላይ፤ ለከባድ ተሽከርካረዎች አጎና ሲኒማ ላይ • ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለገሐር መብራት ላይ • ከንግድ ባንክ ወደ አዲስ አበባ ስቴዲየም ቴሌ መ/ቤት ላይ • ከፒያሳ በአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሀራምቤ ሆቴል ላይ • ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ላይ • ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለገሐር መብራት ላይ • በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎፒምያ ወይም ደንበል አደባባይ ላይ መንገዶቹ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። መረጃው ከተላለፈበት ጊዜ ጀምሮ በተጠቀሱት አካባቢዎች ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርከካሪ አቆሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ዋና ጠቅላይ መምሪያው ገልጿል። አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የጠየቀው ዋና መምሪያው፤ የከተማዋ ህዝብ ሁሌም እያደረገው ላለው ቀና ትብብር ምስጋና አቅርቧል።